Sunday, December 8, 2013

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ወታደራዊ ጥቃት እንደቀጠለ ነው ::!!!!!!!!!!!!

   የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ወታደራዊ ጥቃት እንደቀጠለ ነው
PDF Print E-mail Written
by Administrator Wednesday, 04 December 2013 12:54
የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት ወታደራዊ ጥቃት እንደቀጠለ ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት በወያኔው ታጣቂ ሃይሎች ላይ የማያዳግም እርምጃ እየወሰደ ሲሆን በተሰለፈባቸው አውደ ውጊያዎችም ላይ ከፍተኛ ድል በመቀዳጀት ወታደራዊ የበላይነቱን እያስመሰከረ ይገኛል፡፡ ለአምባገነናዊ ሥርዓት መንኮታኮት ፍቱን መድሃኒቱ የትጥቅ ትግል መሆኑን የተረዳው የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት በሰሜኑ የሀገራችን ክፍሎች በተለያዩ ግንባሮች በመንቀሳቀስ ህዝብንና ሀገርን በማሸበርና በማሰቃየት ተግባር ተመድበው ሕብረተሰቡን ቀፍድዶ በመያዝ አንገቱን ቀና አድርጐ እንዳይራመድ በማድረግ ወያኔያዊ ተልዕኮ ያነገቡ የታጠቁ ሃይሎች ላይ ድንገተኛ የማጥቃት እርምጃ በመውሰድ የግንባሩ ሠራዊት ኢትዮጵያዊ ኩራት መሆኑን በተጨባጭ እያሳየ ሲሆን በህዳር 24 ቀን 2006 ዓ/ም በታች አርማጭሆ ልዩ ስሙ ዕምባ-ጓዳ በተባለው ቦታ መሽጐ በነበረው የልዩ ኃይል ታጣቂ ቡድን ላይ በሰነዘረው ወታደራዊ የማጥቃት እርምጃ ሃያ አንድ (21) የልዩ ኃይል ታጣቂ ቡድኖችን ገድሎ ሃያ ሰባት (27) ያቆሰለ ሲሆን በዚሁ ዕለት በተካሄደው ውጊያ የተለያዩ ከባድና ቀላል መሳሪያዎች ከነመሰል ጥይቶቻቸው ጭምር መማረካቸውንና ከዚሁ ጥቃት ሰለባ ያመለጡት የልዩ ኃይል ታጣቂ ቡድን አባላት ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ሠራዊት የሚሰነዘርባቸውን ጥቃት መቋቋም ተስኗቸው እግሬ አውጪኝ በማለት መሣሪያና ትጥቃቸውን እያዝረከረኩ ለመፈርጠጥ ተገደዋል።
Image

No comments:

Post a Comment